በሊቀ ካህናት ኀይለ ሥላሴ ዓለማየሁ ከአገር መባረር ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ቁጣቸውን እየገለጹ ነውሐራ ዘተዋሕዶ
December 29, 2012
- ሊቀ ካህናት ለጉባኤው መግለጫ ይቅርታ እንዲጠይቁ ለሰዓታት ጫና ተደርጎባቸዋል
- ‹‹አጀንዳዬ ሃይማኖታዊ ነው፤ የሠራኹት ስሕተት ይኹን የምጠይቀው ይቅርታ የለም !!››
- የሰላምና አንድነት ጉባኤው መግለጫ እንደሚያወጣ ይጠበቃል
- መንግሥት በወሰደው ርምጃ የመንበረ ፕትርክና ዓላሚዎቹ ጳጳሳት እጅ እንዳለበት ታምኖበታል
በሊቀ ካህናት ኀይለ ሥላሴ ዓለማየሁ ከአገር መባረር ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ቁጣቸውን እየገለጹ ነውሐራ ዘተዋሕዶ
December 29, 2012
- ሊቀ ካህናት ለጉባኤው መግለጫ ይቅርታ እንዲጠይቁ ለሰዓታት ጫና ተደርጎባቸዋል
- ‹‹አጀንዳዬ ሃይማኖታዊ ነው፤ የሠራኹት ስሕተት ይኹን የምጠይቀው ይቅርታ የለም !!››
- የሰላምና አንድነት ጉባኤው መግለጫ እንደሚያወጣ ይጠበቃል
- መንግሥት በወሰደው ርምጃ የመንበረ ፕትርክና ዓላሚዎቹ ጳጳሳት እጅ እንዳለበት ታምኖበታል
በቀዳሚው የዜና ዘገባችን እንዳስነበብነው÷ ሊቀ ካህናት ኀይለ ሥላሴ ትላንት ከሰዓት በኋላ ፒያሳ ከሚገኘው ቤታቸው ወደ ቦሌ ለስብሰባ ቀጠሮ ብለው ከወጡ በኋላ ነበር ታግተው ቆይተው በዚያው ‹‹ትኬት ተቆርጦላቸው›› ተገደው እንዲወጡ የተደረገው፡፡ የሰላምና አንድነት ጉባኤው ዋነኛው ሰው የኾኑት ልኡኩ በግዳጅ እንዲወጡ ከመደረጋቸው በፊት እስከ ምሽቱ ሁለት ሰዓት ድረስ ባገቷቸው የደኅንነት ኀይሎች በተለያዩ ጥያቄዎችና ተጽዕኖዎች ሲዋከቡ እንደነበር ተገልጧል፡፡ ረቡዕ ዕለት አዲስ አበባ በደረሱበት ወቅትም ሊቀ ካህናትና አብረዋቸው የነበሩት ሌላው ልኡክ በልዩ ክፍል እንዲገቡ ተደርጎ ጥብቅ ፍተሻ እንደተካሄደባቸው ታውቋል፡፡