Wednesday, 7 August 2013

በኮፈሌ የሟቾችና ቁስለኞች ቁጥር ግልጽ አልሆነም


በዋቤ መስጊድ ማን ቦንብ አፈነዳ? ለምን?
kofelie


ባለፈው ዓርብ በመላው አገሪቱ አንድ ወጥ የ”ድምጻችን ይሰማ” የተቃውሞ ድምጽ ለማሰማት የወጣውን መርሃ ግብር ተከትሎ የፌደራል ፖሊስ እስከ ግድያ ሊደርስ የሚችል ርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ የሚያመላክት መግለጫ አውጥቶ ነበር። የድምጻችን ይሰማ አመራር መሆናቸውን የሚገልጹት ክፍሎች ፌደራል ፖሊስ ያወጣውን መግለጫ ተከትሎ ተቃውሞው እንዲቀር መመሪያ ማስተላለፋቸውን ይናገራሉ። በዋቤ መስጊድ ቦንብ ያፈነዳው ማን ነው? ለምን እንዲፈነዳ ተደረገ?
ፖሊስ በከረሩ ቃላቶችና በማስጠንቀቂያ አጅቦ ባወጣው መግለጫ  ” … አክራሪ ወሃቢ ሰለፊዎች ላይ ተገቢውን ክትትል በማድረጉ ፖሊስ ለሚወስደው ርምጃ ተገቢውንና የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪያችንን በድጋሚ እናቀርባለን” በማለት አስፈራርቶ ነበር። “ምንደኛ፣ ከውጪ በሚላክላቸው ንዋይ ዓይናቸው ታውሮ አርብ በመጣ ቁጥር በተመረጡ መስጊዶች ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ጥረት የሚያደርጉ …” በማለት በመግለጫው አስቀድሞ እንደፎከከረው በኮፈሌ ብቻ ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጥፋት መድረሱ ተረጋግጧል።
አስፈላጊውን ድርጊት መርሃ ግብርና የተቃውሞ ደንብ በማስተዋወቅ ከአዲስ አበባ ለአሜሪካ ሬዲዮ መግለጫ የሰጡት አስተባባሪ ኮሚቴ እንዳሉት አቶ መለስ በህይወት እያሉ በ1997 ተቃዋሚዎች ላይ ርምጃ እንዲወሰድ ከሰጡት ትዕዛዝ ጋር ተመሳሳይነት ያለው መግለጫ በመተላለፉ ተቃውሞው እንዲቀር ተደርጓል።
ሰላማዊ የተባለውን ተቃውሞ ከማከናወን ቢቆጠቡም ከአርብ የጁምአ ስግድት አስቀድሞ በየቤቱ በመዘዋወርና በሰላማዊ መንገድ የአምልኮ ስርአታቸውን ለመፈጸም ወደ ተለያዩ መስጊዶች ካቀኑ ምዕመናን መካከል ቀላል ቁጥር የሌላቸው ታስረዋል። ለቪኦኤ መግለጫ የሰጡት የድምጻችን ይሰማ ተወካይ ካንድ ሺህ በላይ ሰዎች መታሰራቸውን አመልክተዋል።
ከመንግስትና የድምጻችን ይሰማ አስተባባሪ ነን ከሚሉት አካላት የሚወጡትን መረጃዎች ሁለት ጽንፍ የያዙ በመሆናቸው በማጣራትና አግባብነት ያለው ትክክለኛ መረጃ ለመስጠት የዝግጅት ክፍላችን ተቸግሯል። በዚህም የተነሳ የተሟላ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት እንዳለ ሆኖ ባብዛኛው ዘገባችን ከማህበራዊ ገጽ በሚገኙ ዜናዎችና ከመንግስት ድረገጾች እንዲሁም ከአሜሪካ ሬዲዮ ባገኘነው መረጃ የተወሰነ ሆኗል።

Tuesday, 6 August 2013

Preying and Praying: A Day and Night with the EPRDF

August 6, 2013

by Faysal Qassim
During the day on August 3, 2013, the Ethiopian government was unusually busy in its anti-Muslim operations. As night time came, however, the government immediately took a likewise unusual pro-Islam face. The Ethiopian state TV aired a special congregational Muslim ritual held on the 27th of the Holy Month of Ramadan. This abrupt shift in the regime’s apparent behavior may surprise some, amuse others, but surely shock many.
Ethiopian Television live streaming.
It is striking to note that the live broadcast took place by the end of that same day when the government went crazy with its killing spree and massive arrests. According to many credible sources, the government had by then killed at least 11 people in Oromia region of Ethiopia, and arrested thousands for no apparent reason other than their assertiveness in demanding their constitutional rights. The aim of the uncanny night-time transmission is thus obvious: neutralizing the fast developing anti-Islam and anti-Muslim image of the ruling party in the eyes of its Muslim citizens.
This attempt at revamping public image is both bizarre and shocking. How would any government truly believe in the efficacy of an arbitrary, ephemeral and cosmetic measure as a panacea to the awful damage it perpetrated on its people? The government’s reasoning is not just quite amazing, however, but also utterly shocking. It lays bare the deeply condescending attitude of the EPRDF towards its Muslims citizens. If it really expected such a TV transmission would amount to anything positive politically, then it would be one more clear proof that the core of the party is infested with a chronic illness of toxic contempt for people.

Monday, 5 August 2013

የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ እና የመቀሌያችን መታፈን ከነመፍትሄው!

August 5, 2013


ግርማ ሞገስ (girmamoges1@gmail.com)
ሰኞ ሐምሌ 29 ቀን 2005 ዓ.ም.

የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ ወደፊት በመገስገስ ላይ ይገኛል። አንድነቶች የኢትዮጵያን ጸረ-ሽብር ህግ ለማሰረዝ የዜጎች ፊርማ በማሰባሰብ ዘመቻ ላይ ናቸው። የቀድሞውን የግብጽ ፕሬዘዳንት ሞርሲን ከስልጣን የማውረድ እንቅስቃሴ ያስጀመረው ከአስራ አምስት ሚሊዮን በላይ የሚገመተው የግብጾች ፊርማ ከተለያዩ ከተሞች የተሰበሰበው በሶስት ወሮች ነበር። በግብጾች አይን ሲታይ አንድነቶች በሶስት ወሮች አንድ ሚሊዮን ፊርማ ማሰባሰብ አይችሉም ብለን መገመት ያዳግተናል። እርግጥ ኢትዮጵያውያን በሰላማዊ ትግል ባህል እና ክህሎት እንደ ግብጾች ብዙ አልዘለቅንም። ይሁን እንጂ ካሰብነው ቁጥር እንደምንደርስ ጥርጥር የለኝም። የአንድነት መሪዎች መታሰር ቢደርስባቸውም የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት የመጀመሪያው ዘመቻ በጎንደር እና በደሴ ከተሞች ሐምሌ 7 ቀን በስኬት ተፈጽሟል። በጎንደር እና በደሴ ከተሞች የዜጎች ፊርማዎች ተሰብስበዋል።
Millions of voices for freedom - UDJ
ባለፈው ሳምንት ደግሞ አንድነቶች የየከተሞች አስተዳዳሪዎች እና የጸጥታ ኃይሎች የሚፈጽሙባቸውን የወከባ፣ የመኪና ጎማ በማስተንፈስ መጓጓዣ የማሳጣት፣ የቢሮክራሲ ጫና፣ የአካል ድብደባ እና እስር የተለመደ ጽዋቸውን በቻይነት እና በሆደ ሰፊነት በመቀበል እሁድ ሐምሌ 28 ቀን ከመቀሌ በስተቀር በወላይታ፣ በጂንካ፣ በአርባምንጭ እና በባህርዳር ሁለተኛውን ዘመቻ በስኬት አጠናቀዋል። ይኽን በውጣ ውረድ የተሞላ ዘመቻ አንድነቶች ሳይታክቱ፣ በትዕግስት፣ በፅናት፣ በአርቆ አስተዋይነት እና በድስፕሊን በታነጸ አኪያሄድ ፈጽመዋል። አንድነቶች “አንድነት ፓርቲ ሳይገድል እየሞተ ህገ-መንግስቱን የማስከበር ትግሉን አጠንክሮ ዛሬም ወደፊትም ይቀጥላል፡፡” የሚሉትን መርሃቸውን ምንም ሳይሸራረፍ በተግባር እየፈጸሙት ነው። ከህዝባቸው ጋር ታግለው ህዝባቸውን የመብቱ ባለቤት ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኛነት እያሳያዩን ነው። ሊመሰገኑ ይገባል። በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ እንደሚባለው በአንድ ወገን ፀር-ሽብር ህጉን ለማሰረዝ ሰላማዊ ትግል ዘመቻ ስታደርጉ በሌላ በኩል ደግሞ ከቀድሞው የመገዳደል የፖለቲካ ትግል ባህላችን ወደ ሰላማዊ ፖለቲካ ትግል ባህል ልታሸጋግሩን ታሪክ እየሰራችሁ ነው። ይኽን ሁሉ የምታደርጉት በአስጨናቂ እና በተስፋ አስቆራጭ ሁኔታ ውስጥ እንደሆነ ህዝባችሁ ይረዳዋል። የኢትዮጵያ ጉዳይ የሚያሳስበው በአገር ውስጥ እና ካገር ውጭ የሚኖረው ህዝባችሁ ስራችሁን በአክብሮት፣ በአድናቆት እና በኩራት እያስተዋለ ነው። በስራችሁ እና በስኬታችሁ ልትደሰቱ ይገባል። ታሪክ እየሰራችሁ ነው።

Sunday, 4 August 2013

ዛሬ በባህርዳር ከተማ ዝናብ እየዘነበም ቢሆን ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ያለው ምስል በከፊል

August 4, 2013


ፍኖተ ነፃነት
መፈክሮች፣
ያማራው ህዝብ ጨዋ እንጂ ፈሪ አይደለም!
ለሱዳን ተቆርሶ የተሰጠው መሬታችን ይመለስ!
የሙስሊም መፍት ሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ባስቸኩዋይ ይፈቱ!
እስክንድር ነጋ ጋዜጠኛ እንጂ አሸባሪ አይደለም።!
የመሳሰሉት መፈክሮች ተሰምተል!
Bahir Dar Demonstration against T.P.L.F UDJ

Breaking News Genocide in Totolamo Village, Ethiopia


The Horn Times Breaking News August 4, 2013
by Getahune Bekele-South Africa

Genocide: 11 Ethiopian Muslims mowed down in the Totolamo village blood bath
August 4, 2013
A five year old kid, an elderly imam and four teens are among the dead
The small maize and potato farming Muslim village of Totolamo in south west oromiyya near the strategic town of Shashemene is in deep mourning after 11 of her citizens gunned down in cold blood by the genocidal Tigre People Liberation Front/ TPLF federal police commandos on Saturday August 3, 2013.
A five year old kid, an elderly imam and four teens are among the dead according to information obtained from Shashemne general hospital where the bodies are stashed in a tiny morgue. The number of the wounded is still unknown.
The fate of hundreds who took refuge inside the Erob Gebya Mosque in the troubled village and surrounded by the federal police is also not yet known. Several others are in detention at the nearby Kofele town police station and the town along with Totolamo village is under total control of the TPLF gunmen in police uniform. Today August 4, 2013 residents are warned to stay indoors as the situation remain frighteningly tense.

Thursday, 1 August 2013

ወያኔ በሰላማዊ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላይ ጥቃት ለመፈጸም ተዘጋጅቻለሁ ብሏል

August 1, 2013


ወያኔ ነገ ሙስሊሞች ተቃውሟቸውን የሚቀጥሉ ከሆነ እርምጃ እወስዳለው የሚል መግለጫ አውጥቷል። 

ነገ በአዲስ አበባ ፍልውሃ “ቶፊቅ መስጂድ” እና በተለያዩ የክልል ከተሞች ሙስሊሞች የተለመደ ተቃውሟቸውን ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።


ኢሳት ይህንን አስመልክቶ እንደሚከተለው ዜናውን አቅርቦታል።

ኢትዮ-ኤርትራ፣ ኤሌክትሪክ እንደ መደራደሪያ?

ኢትዮጵያ የኤርትራን መንግስት ወደሰላማዊ የድርድር መድረክ ለማቅረብ 250 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል በነጻ ለመስጠት አስባለች መባሉንየሚጠቁም ዜና በድረገጾች እየተነበበ ነዉ።

የኤርትራ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትርን በስም በመጥቀስ የቀረበዉ ዘገባ፣ በሎንዶን ለሚገኙ የኤርትራ ማኅበረሰብ ንግግር አሰሙ ያላቸው ኤርትራዊ ሚንስትር ሁለቱ ሃገሮች ወደጤናማ ግንኙነት የሚገቡት ኢትዮጵያ በኃይል ከያዘቻቸዉ የኤርትራ ግዛቶች ስትለቅ ነዉ ማለታቸዉን ያትታል። የኢትዮጵያ መንግስት ዘገባዉን አስተባብሏል፤ ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር የሚመለከታቸዉን የመንግስት አካላት በማነጋገር ዘገባ ልኮልናል። የተሰራጨዉን ዘገባ በመጥቀስ ወደአስመራ ደዉለን ያነጋገርናቸዉ በኤርትራ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚኒስቴር ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር፤ አቶ ጸሀዬ ፋሲልም የተጀመረ ድርድርም የለም የኤሌክትሪክ ኃይል የመስጠት ሀሳብ ቀርቦዋል ስለመባሉም መንግስታቸዉ የሚያዉቀዉ እንደሌለ ገልጸዉልናል።
ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ

AUDIOS AND VIDEOS ON THE TOPIC