Ethiopian People's Revolutionary Party Women
Thursday, 7 March 2013
ሁለት የኢትዮጵያ አትሌቶች ውድድራቸውን አቋርጠው ጠፉ
የካቲት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-
ሀአሬጽ የተባለው የእስራኤል ጋዜጣ እንደዘገበው ሁለቱ አትሌቶች የማራቶን ሩጫቸውን በማቋረጥ ነው ባለፈው አርብ ፣ ማርች 1፣ 2013 የጠፉት።
ሜላት መኮንን እና ማህሌት ዘለቀ የተባሉ የ24 እና 25 አመት እድሜ ያላቸው አትሌቶች የጠፉት በደቡብ ቴላቪቭ ሲሆን፤ የ እስራኤል ፖሊስ አትሌቶቹ ሆን ብለው እንደጠፉ ገልጿል።
ሁለቱም አትሌቶች ፓስፖርታቸውን እና ሌሎች እቃዎቻቸውን ሁሉ በመተው በሩጫ ልብሳቸው መጥፋታቸውን ፖሊስ አስታውቋል።
አትሌቶቹ እስካሁን ለፖሊስም ሆነ ለአካባቢው ባለስልጣናት ስለሁኔታው አላመለከቱም።
No comments:
Post a Comment
Newer Post
Older Post
Home
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment