Thursday, 7 March 2013

ሁለት የኢትዮጵያ አትሌቶች ውድድራቸውን አቋርጠው ጠፉ




የካቲት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም 



ኢሳት ዜና:-ሀአሬጽ የተባለው የእስራኤል ጋዜጣ እንደዘገበው ሁለቱ አትሌቶች የማራቶን ሩጫቸውን በማቋረጥ ነው ባለፈው አርብ ፣ ማርች 1፣ 2013 የጠፉት። ሜላት መኮንን እና ማህሌት ዘለቀ የተባሉ የ24 እና 25 አመት እድሜ ያላቸው አትሌቶች የጠፉት በደቡብ ቴላቪቭ ሲሆን፤ የ እስራኤል ፖሊስ አትሌቶቹ ሆን ብለው እንደጠፉ ገልጿል።
ሁለቱም አትሌቶች  ፓስፖርታቸውን  እና ሌሎች እቃዎቻቸውን ሁሉ በመተው በሩጫ ልብሳቸው መጥፋታቸውን ፖሊስ አስታውቋል። አትሌቶቹ እስካሁን ለፖሊስም ሆነ ለአካባቢው ባለስልጣናት ስለሁኔታው አላመለከቱም።

No comments:

Post a Comment