ሂዉማን ራይትስ ዎች ኢትዮጵያ ዉስጥ ይደረጋል ያለዉን የቴሌፎንና የኢንተርኔት ቁጥጥርና ስለላ የተመለከ ዘገባ ይፋ አደረገ።
ዘገባዉ በዉጭ ሀገር መንግስታት ቴክኒዎሎጂ እና በእነሱም ርዳታ እንዲሁም በደረሱበት እድገት ተደግፎ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚንቀሳቀሱትን ሕዝባዊ ድርጅቶች፣ ጋዜጠኞችና የተቃዉሞ ፓርቲ አባላትን፣ ተማሪዎችንና የሙያ ማኅበራት አባሎችን የኢትዮጵያ መንግስት ይከታተላል የሚል ነዉ። በዉጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንንም እንዲሁ ተከታትሎ ስልካቸዉን በመጥለፍ፣ ኮምፕዩተራቸዉን በርብሮ የግል ምስጢራቸዉን ይከታተል በማለት ሂዉማን ራይትስ ዎች ድርጊቱን ኮንኗል። የድርጅቱን ጋዜጣዊ መግለጫ የተከታተለዉ የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለሚካኤል ዝርዝሩን ልኮልናል። በርሊን የሚገኘዉ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዓለም ዓቀፉ የመብት ተm።ጋች ድርጅት ሂዉማን ራiteስ ዎች ስላወጣዉ ዘገባ ያለዉን አስተያየት እንዲሰጥ በርሊን የሚገኘዉ ዘጋቢያችን በተደጋጋሚ ጠይቆ ነበር ሆኖም የኤምባሲዉ ባልደረቦች መልሰን እንደዉላለን ቢሉም ስቱዲዮ እስከገባንበት ጊዜ ድረስ ምላሻቸዉን አላገኘንም።
ይልማ ኃይለሚካኤል
ሸዋዬ ለገሠ
ነጋሽ መሐመድ
No comments:
Post a Comment